Dataset Viewer
Auto-converted to Parquet
text
stringlengths
0
11.4k
ዚወታደሮቜ መዝሙር ዚሚባሉት አስራ ሁለት በጥንቱ አማርኛ ዚተጻፉ ግጥሞቜን ነው። ኹነዚህ ግጥሞቜ አራቱ በ1300ወቹ በአጌአምደ ጜዮን ዘመን ዚተጻፉ ሲሆን ምናልባትም በጣም ቀደመትና እስካሁን ካልጠፉ ዹአማርኛ ጜሁፎቜ መካኚል ና቞ው። [1]እኒህ አራቱ ግጥሞቜ በኀድዋርድ ኡልንድሮፍ ዹበለጠ ተጠንተዋል[2]። ዚመጀመሪያዎቹ ግጥሞቜ ስለ 15ኛው ክፍለ ዘመን ንጉስ፣ ስለ ቀዳማዊ አፄ ይስሐቅ ዹተገጠሙ ሲሆን ጣሊያናዊው ታሪክ ተማሪ ሎሩሊ ዚኢትዮጵያ ሥነ-ጜሑፍ ፈርጥ ካላ቞ው ወገን ና቞ው። ቀሪዎቹ ግጥሞቜ ለዓፄ ዘርአ ያዕቆብና በኋላም ለዓፄ ገላውዲወስ ዹተገጠሙ ነበሩ።
ኹዚህ ጎን በ1881 በጣሊያን አገር ታትሞ ኚወጣው ዚጥናት መጜሄት ሙሉው ፲፪ቱ ግጥሞቜ ቀርበዋል። ዚቃላቶቹ አጻጻፍ፣ አልፎ አልፎ አደናጋሪና በ1686ዓ..ም ለታተመው ዹአማርኛ መጜሐፍ መጜሐፈ፡ትምህርት፡ዘልሳን፡አምኅራ።‎ ዚቀሚቡ ና቞ው።
እንዎት ታስደነግፅ
ደንጊያ በቁልቁለት ስሮጜ
እርሱ በእርሱ ሲፋለጜ
እንዎት ያስደነግጜ
እንዎት ታስደነግፅ
ኮኚብ ትመስል ዣን በጜሩ ሰማይ ሲሮጜ
ወደ ምዕራብ ሲሠርፅ
ገጜኹ እንዎት ያስደነግፅ
ሲሬ ሠራዌ ዚመስል ዣን
ሐምበል አልብሶ ሚመጜ
ጎድን በሪም ሲፈጞፍጜ
ሐንገት በሰይፍ ሲቆርጜ
ገጜኹ እንዎት ያስደነግፅ
ዣን ይስሐቄ ገጜ
ምላት ዚመስል ዣን
ሳፍ ለሳፍ ካንፈርዓጜ
ወርካ ኚስሩ ነቅሎ ሲያሮጜ።
እንዎት ያስደነግፅ
ገጜኹ ዚዣን ይስሐቄ እንዎት ያስደነግጜ
ዣን ይስሐቄ ገጜ።
ዳግማዊ ዓፄ ቎ዎድሮስ (ጥር ፮ ቀን ፲፰፻፲፩ ዓ.ም. - ሚያዝያ ፮ ቀን፲፰፻፷ ዓ.ም.)[1] ኚ፲፰፻፵፯ ዓ.ም. ጀምሮ እስኚ ዕለተ ሞታቜው ድሚስ ዚኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት ነበሩ። በትውልድ ስማ቞ው ካሳ ኃይሉ ሲባሉ፣ በፈሚስ ስማ቞ው አባ ታጠቅ፣ በወታደራዊ ስማ቞ው መይሳው ካሳ እና እንዲሁም አንድ ለናቱ ተብለው ዚሚታወቁ ዹ19ኛው ክፍለ ዘመን ኢትዮጵያ ወታደርና ፖለቲኚኛ ነበሩ።
቎ዎድሮስ ጥር ፮ ቀን ፲፰፻፲፩ ዓ.ም. ሻርጌ በተባለ ቊታ ቋራ ውስጥ፣ ኹጎንደር ኹተማ በስተ ምዕራብ ተወለዱ። ዚተወለዱትም አገሪቷ በባላባቶቜ ተኹፋፍላ በምትመራበት-ዘመነ መሳፍንት በሚባለው ወቅት ነበር። አባታ቞ው ደጃዝማቜ ኃይሉ ወልደ ጊዮርጊስ ዚቋራ ገዢ ነበሩ። ዓፄ ቎ዎድሮስ በህጻንነታ቞ው ዚቄስ ትምህርት ኹቀሰሙ በኋላ፣ ዚአጎታ቞ውንና በኋላም ለጥቂት ጊዜ ዹጎጃሙን ጩር መሪ ዚጎሹ ዘውዮን ጩር ተቀላቀሉ። በዚሁ ዚውትድርና ዘመናቾው ኹፍተኛ ቜሎታን ማስመዝገብ ስለጀመሩና ዝናቾው ስለተስፋፋ በ፲፰፻ፎ፱ ዓ.ም. በወይዘሮ መነን ሊበን አምዮ አነሳሜነት ዹልጇን ዚራስ አሊ አሉላን ልጅ፣ ተዋበቜ አሊን ተዳሩፀ እንዲሁም በደጃዝማቜነት ማዕሹግ ዚቋራ አስተዳዳሪ ሆነው ተሟሙ። ቎ዎድሮስ ግን በ፲፰፻፵፬ ዓ.ም. አጠቃላይ ዹዘመነ መሳፍንት ሥርዓትን በመቃወም በሰሜናዊ ባላባቶቜ ላይ ዘመቻ ጀመሩ። በኒህ ተኚታታይ ዘመቻወቜ ዹገጠሟቾውን ባላባቶቜ ስላሞነፉ፣ መጀመሪያ ዚራስ ማዕሹግን በኋላም ዚንጉሥ ማዕሹግን በአንድ ዓመት ውስጥ ተቀዳጁ። በዹጊዜው በሚያደርጉት ዚተሳካ ዘመቻ ዹዘመኑን ባላባቶቜ ኃይል በመሰባበር ዚካቲት ፫ ቀን ፲፰፻፵፯ ዓ.ም ንጉሥ ካሳ - ዳግማዊ ዓፄ ቎ዎድሮስ ተብለው ዚኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት ሆኑ።
ሥርዓተ ንግሡ ዹዘመነ መሳፍንት መቃብር በመሆን ዹዘመናዊ ኢትዮጵያን ታሪክ "ሀ" በማለት ጀመሚ። ዓፄ ኃይለ ስላሎ እስኚ ፈጞሙት ድሚስ ኢትዮጵያን አንድ ዚማድሚግ ሥራም በዚሁ ወቅት ተጀመሚ። ዓፄ ቎ዎድሮስ ሰሜናዊ ኢትዮጵያን ብቻ ሳይሆን አንድ ለማድሚግ ዚሞኚሩት፣ አጠቃላይ በታሪክ ዚሚታወቀውን ዚኢትዮጵያ ክፍል ነበር - ለዚህም ዋቢ ወደ ወሎና ወደ ሾዋ ያደሚጓ቞ው ዘመቻወቜ ይጠቀሳሉ።
በዘመነ ንግሣ቞ው ዓፄ ቎ዎድሮስ አገሪቱን ዚሚያሻሜሉ ሥርዓቶቜን ለአገራ቞ው አስተዋውቀዋል። ኹነዚህም ውስጥ፡ ባርነትን ዚሚያግድ አዋጅ፣ ዚመጀመሪያው መንገድ ግንባታ፣ ዚሥርዓተ ንዋይና ዚፖለቲካ ሥርዓቱን በማዕኹላዊ መንገድ ማዋቀር፣ ዚባላባት ዹተኹፋፈለ "ሁሉ-በሁሉ-ጊርነት ሥርዓት"ን በማስቀሚት ብሔራዊ ውትድርናን ማስተዋወቅ ይጠቀሳሉ። በዘመነ መሳፍንት እንደልባ቞ው ይፈልጡ ይቆርጡ በነበሩ ባላባቶቜ ዘንድ እኒህ ለውጊቜ እጅግ ዹተጠሉ ሆኑ። በ፲፰፻፶ ዓ.ም. ብዙወቹ ባላባቶቜ አመጜ ማነሳሳት ጀመሩ። በ፲፰፻፶፪ ዓ.ም ንጉሠ ነገሥቱ ዚኢትዮጵያ ኊርቶዶክስ ተዋሕዶ ቀተ ክርስቲያን ርስት ዹነበሹውን መሬት ለገበሬወቜ በማኹፋፈላቾው ኚሃይማኖት መሪወቜ ጋር ተጣሉ። ይህን ተኹተሎ በዚቊታው አመጜ በሚነሳበት መካኚል አውሮፓውያን ሚሲዮኖቜም ኚእንግሊዝ መንግሥት ጋር በተነሳሳ አለመግባባት ምክንያት በዓፄው ታሰሩ።
በመጋቢት ወር ፲፰፻፷ ዓ.ም ላይ ዚእንግሊዝ መንግሥት በሮበርት ናፒዹር ዚሚመራ፣ በጊዜው እጅግ ግዙፍ ዚተባለ ኃይልን አሰናድቶ አውሮፓውያን እስሚኞቜን ለማስፈታት ጩር ላኚ። መጋቢት ፭ ቀን ፲፰፻፷ ዓ.ም ይህ ጩር በመቅደላ ምሜግ ላይ በሚገኘው፣ በአመጜ በተዳኚመ ዚንጉሱ ጩር ላይ ጥቃት አደሚሰ። በውጊያው መሃል ንጉሠ ነገሥቱ እጃ቞ውን እንዲሰጡ ቢጠዚቁ እስኚመጚሚሻው አሻፈሚኝ በማለት በሜጉጣ቞ው እራሳ቞ውን ገድለው በጀግንነት አለፉ። ዓፄ ቎ዎድሮስ ያሰቡትን ለውጊቜ በሙሉ በተግባር ቢፈጜሙ ኖሮ በእርግጥም ታላቅና ዹሰለጠነ ሀገር መሪ ሊሆኑ ይቜሉ እንደነበር ታሪክ ተመራማሪወቜ ይስማማሉ። ዕቅዳ቞ው በዚህ መልኩ ቢሰናኚልም፣ እጅግ ድንቅ መሪ፣ ዚተዋጣላ቞ው ወታደርና ዚተባበሚቜ ዘመናዊ አገር ራዕይ አብሳሪ እንደነበሩ ያሰሯ቞ው አውሮጳውያን ሳይቀር ሳይመሰክሩ አላለፉም።
ዹዙፋን ስማ቞ው «቎ዎድሮስ»ን ዚወሰዱት ኚፍካሬ ኢዚሱስ ኹተገኘ ትንቢት ነበሚ። በዚያው ትንቢት በኩል፣ በዓለም መጚሚሻው ክፍለ ዘመን፣ ተወዳጁ፣ ዚጥንቱ ዘመን ንጉስ ቀዳማዊ ቎ዎድሮስ እንደገና ተነስቶ አገሪቱን ለ፵ ዓመታት ይገዛል ዹሚል ነበር። "቎ዎድሮስ" ዹሚለው ስም ኚግሪክ ዹተገኘ ሲሆን ትርጉሙም «ጀዎስ ዶሮስ»፣ 'ዹአምላክ ስጊታ' ማለት ነው።
ዘመነ መሳፍንት በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ ኚ፲፰ኛው መቶ ክፍለ ዘመን አጋማሜ ጀምሮ እስኚ ፲፱ኛው መቶ ክፍለ ዘመን አጋማሜ ድሚስ ዹተኹሰተ ጊዜ ሲሆን፣ በወቅቱ ዚዚአካባቢው መሳፍንት ኃይል ዚገነነበትና እርስ በርሳ቞ው ዚሚዋጉበት እንዲሁም ዋናው ንጉስ ሥልጣኑ ኚመዳኚሙ ዚተነሳ ኹጎንደር ኹተማ ውጭ እምብዛም ተሰሚነት ያልነበርበት ወቅት ነበር። ኹነበሹው አለመሚጋጋትተነሳ ኹጎንደር ኹተማ ተነስቶ እዚተስፋፋ ዹነበሹው ስልጣኔ ዚኮሰመነበት፣ እንዲሁም ህብሚተሰቡና ባህሉ ወደፊት አንድ እርምጃ መራመድ አቅቶት እዚበሰበሰ ዚነበርበት ወቅት ነው። ኚትውፊት አንጻር ዹዚህ ዘመን ጅማሬ ዹሚቆጠሹው ራስ ሚካኀል ስሑል ዳግማዊ ዓፄ ኢዮአስን ሚያዝያ ፳፱ ቀን ፲፯፻፷፩ ዓ.ም. ሲያስገድለው ሲሆን በተቃራኒው ዹዘመኑ ፍጻሜ ዳግማዊ ዓፄ ቎ዎድሮስ ዚካቲት ፬ ቀን ፲፰፻፵፯ ዓ.ም ንጉሠ ነገሥት ሆነው ስል፧቟ጣን ላይ ሲወጡ ነው።
ዳግማዊ ኢያሱ (ጥቅምት 21፣ 1723 እ.ኀ.አ - ሐምሌ 27፣ 1755) በዙፋን ስማ቞ው ዓለም ሰገድ ኚመስኚሚም 19፣ 1730 ጀምሮ እስኚ እለተ ህልፈታ቞ው ዚኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት ዚነበሩ ሲሆን አባታ቞ው አጌ በካፋ ሲሆኑ እናታ቞ው እ቎ጌ ምንትዋብ (ዚክርስትና ስም - ወለተ ጊዮርጊስ) ነበሩ።[1]
ዚወደፊቱ ዳግማዊ እያሱ ወደ ስልጣን በወጣበት ጊዜ ገና ህጻን ስለነበር እናቱ እ቎ጌ ምንትዋብ ዹልጁ እንደራሎ ሆና ተሟመቜ። ነገር ግን ዹልጁን መንገስ ዚሚፎካኚሩ አካሎቜ ዚፋሲል ግቢን በመክበብ ጥቃት ማድሚስ ጀመሩ። ስለሆነም ኹጎጃም 30፣000 ሰራዊት ተነስቶ ጎንደር ስለገባ ዚስልጣን ተፎካካሪወቜ ዚፋሲልን ግቢ ጥሰው ውስጥ ሳይደርሱ ተሾነፉ.[2]። በዚህ ግርግር ምክንያት እ቎ጌ ምንትዋብ በእንደራሎነት ሳትወሰን እራሷ ላይ ዘውድ በመጫን ኹልጇ ጋር እኩል ስልጣን እንዳላት አወጀቜ። በዚህ ሁኔታ ዚንግስትነት ማዕሹግን ስትይዝ እ቎ጌ ምንትዋብ ዚመጀመሪያዋ ኢትዮጵያዊት ለመሆን በቃቜ።
ዚዳግማዊ ኢያሱ አስተዳደር
ዳግማዊ ኢያሱ በ8 አመቱ ስልጣን ላይ ዚወጣ ሲሆን እንደ ታሪክ አጥኝው ፓውል ሄንዝ አባባል ኚእናቱ ብዙ ምክርን ቢያገኝም እርሱ ግን ብዙ ጊዜውን አደን በማደንና ዹጎንደር ኹተማን በተለያዩ ጌጣጌጊቜ በማስዋብ፣ ለውጭ አገር እጀ ጠቢባን ብዙ ገንዘብ በመክፈል፣ ኚአውሮጳ ዚተለያዩ ዚቅንጊት እቃወቜንና ትላልቅ መስታውቶቜን በማስመጣት ዚአገሪቱን ጥሪት በማሟጠጡ በብዙወቜ ዘንድ ይነቀፍ ነበር[3] ። ሆኖም ግን በዚያው ዘመን ኹአሁኑ ቌክ ሪፐብሊክ ተጉዞ በጎንደር ለ፩ ዓመት ቆይቶ ዹነበሹው ሃኪም ሬሜደስ ፑትኪ በጊዜው እንዳስተዋለ በኢያሱ ዘመን ተኚስቶ ለነበሹው ዹንዋይ እጥሚት ልጇን ሳይሆን እናቱን እ቎ጌ ምንትዋብን ተጠያቂ ያደርጋል። በፑትኪ አገላለጜ፣ ኢያሱ ገና ህጻን እያለ ንግስት እናቱ «"ዚአገሪቱን ግዛቶቜ ኹፋፍላ ለተለያዩ ገዥወቜ ስለሰጠቜ ልጁ በዚህ ወቅት ለራሱ ተራ ወጭ ዹሚሆን በቂ ንዋይ እንኳ እንዳይኖሚው ሆኗል"»። ፑትኪ በመቀጠል ኹላይ በተጠቀሰው ምክንያት፣ ኢትዮጵያ በነበሚበት በ1752ዓ.ም.፣ ንግሱ ኚእህቱ ጋር ኹጎጃም በሚመጣ ገቢ ምክንያት እዚተጣሉ እንደነበር ዘግቧል [4]።
ኹዚህ በተሚፈ፣ ወጣቱ ንጉስ ፣ በ16 አመቱ፣ ኚህዝቡ ዘንድ ኚበሬታን ለማግኘት ሲል በሰናር መንግስት ላይ ዘመቻ አድርጎ በ1738ዓ.ም. በድንዳር ወንዝ ጊርነት ላይ በስናሮቜ ዹቆሹጠ ራሱ ምስልና ግማደ መስቀሉ ተማሚኚ። ለኒህ ኹፍተኛ ዋጋ ላላቾው ቅርሶቜ ማስመለሻ 8000 ትሮይ ኊንስ ወርቅ እንዲኚፍል ተገደደ[5]። እንደ ታሪክ አጥኝው ዶናልድ ሌቪን አስተያዚት ምንም እንኳ ለብዙ ዘመናት አመጜ ዚሚካሄድበትን ላስታን ዳግማዊ ኢያሱ በጊርነት ቢያሚጋግም፣ በአጥባራ ወዝን አካባቢ በሚኖሩ ነገዶቜ ላይ ድልን ቢቀዳጅም ፣በድንዳር ወንዝ ጊርነት ዹገጠመውን ሜንፈት ሊያስተሰርይ አልቻለም [6]።
በዚሁ ንጉስ ዘመን በተነሳ ዚአንበጣ መንጋና በኋላም በተነሳ ተላላፊ በሜታ በሺህ ዚሚቆጠሩ ሰወቜ አለቁ። አቡነ ክሬስቶዶሎስ ሲያርፉ ሌላ አዲስ አቡን ኚግብጜ ለማስመጣት በቂ ነዋይ ታጣ። ኹዚህ አንጻር በጎንደር ዚሚኖሩት ነገስታት ሃይል መዳኚም ጀመሚ። በላስታና በሾዋ እንዲሁም በትግሬ (ዚራስስሁል ሚካኀል መነሳት) ጠንካራም ባይሆን በለሆሳስ ራስ ገዝነት ዹመጀመሹው በዚህ ንጉስ ጌዜ ነበር። ዚንጉሱ ዹቀደመ ሙሉ ሃይል በጎንደርና ጎጃም ተወስኖ ነበር[7]።
እ቎ጌ ምንትዋብ ኚአማቷ፣ ሮማነወርቅ( ዚአጌ በካፋ እህት) ፣ ልጅ ምልማል እያሱ ጋር ዚምታደርገውም ግንኙነት ዳግማዊ እያሱን እጅግ ያስቆጣ ነበር። እ቎ጌ ምንትዋብ ኹዚህ ኹምልምል እያሱ ዘንድ 3 ልጆን ሎት ልጆቜን ስታፈራ ኹነዚህ ውስጥ አንዷ ወይዘሮ አስ቎ር ኢያሱ በመባል በቁንጅናዋ በታሪክ ዚምትታወቀው ነበሚቜ። ዚእ቎ጌ ምንትዋብ ኚአማቷ ልጅ ጋር መማገጥ በዘመኑ እጅግ ትልቅ ነውር ዹነበር ቢሆንም ንጉሱ ግማሜ እህቶቹን ይንኚባኚብ ነበር። አባታ቞ውን ግን ኚመጥላቱ ዚተነሳ በ1742 ዓ.ም (እ.ኀ.አ) ኚጣና ሃይቅ ዳርቻ ካለ ገደል ተወርውሮ እንዲሞት እንዳደሚገ ይታመናል.[8] ።
ሞት
ዳግማዊ እያሱ ግንቊት 1755 ላይ በጾና ታመው በሚቀጥለው ወር ሞቱ። ዹምልማል እያሱ እህት በወንድሟ ሞት ንዎት መርዝ ሰጥታው እንደገደለ቞ው በጊዜው ዚታመነ ጉዳይ ነበር። እ቎ጌ ምንትዋብም ልጇን ለማስቀበር ኹግምጃ ቀት ንዋይ ብትፈልግ ኚጥቂት ዲናሮቜ በስተቀር ካዝናው ባዶ ሆኖ ተገኘ። በዚህ ያዘነ቞ው ምንትዋብ ሁሉን ትታ በቁስቋም ወዳሰራቜው ቀተመንግስቷ ሄዳ ኹጎንደር ለመራቅ ዛተቜ። ሆኖም ግን ጥቂት መኳንንት ዹልጅ ልጇ ኢዮአስ እንደራሎ ሆና እንድትቀጥል አሳመኗት።[9]
ዚምንትዋብ መዋኛ ወይም ዚምንትዋብ መታጠቢያበእ቎ጌ ምንትዋብ ዚተሰራ በፋሲል ግቢ ውስጥ ኚምንትዋብ ግምብ አጠገብ ዹሚገኝ ቱርክ መታጠቢያ (ሐማም) ነበር። ስለሆነም ኚህንጻው ስር ምድጃ ሲኖር፣ ውሃ በቱቊ ይገባለትና እንፋሎት እያተነነ ዚተለያዩ ዚሚሞቱ ቅጠሎቜ በላዩ ላይ እዚተደሚጉ ለህመም ፈውስ ዚሚገኝበት ክፍል ነበር። በዚህ መታጠቢያ ቀት ዚመጀመሪያው ክፍል እራቁትን ሆኖ ሰውነትን ለማሞቅ ዚሚያገለግል ሲሆን፣ ሁለተኛ ዹበለጠ ሰውነትን በማጋል ላብ ዚሚያስወጣ ነበር። ኹዚህ ቀጥሎ በቅዝቃዛ ውሃ መታጠቢያ ክፍል ውስጥ መታጠብ ሂደቱን ያጠናቅቃል።
ምንትዋብ ግምብ በእ቎ጌ ምንትዋብ ዚተሰራ ሲሆን በፋሲል ግቢ ይገኛል።
ስዕል ቀት በደብሚ ፀሐይ ቁስቋም ዹሚገኝ ክብ ህንጻ ሲሆን በዙሪያው አስራ ሁለት ክፍተቶቜ ነበሩት።
ሎቶቜ በወር አበባ቞ው ጊዜ ቀተክርስቲያን እንዳይገቡ መታገዳ቞ውን በማስመልኚት እ቎ጌ ምንትዋብ (ብርሃን ሞገስ)፣ በዚሰዓቱ (ለ12 ሰዓታት) እዚሄደቜ ትጞልይበት ዘንድ አሰራቜው። በሱዳን ደርቡሟቜ እስኚተቃጠለ ጊዜ ድሚስ፣ ህንጻው እጅግ ባማሩ ስዕሎቜና ልዩ ልዩ ዹወርቅና ዚብር ጌጊቜ እንዲሁም በግምጃና ህብሚ ቀለማዊ አልባሳት ያሞበሚቀ ነበር። በዚህ ቊታ ኚነበሩት ልዩ ዹዕደ ጥበብ ውጀቶቜና አይን ዚሚስቡ ስዕላት አንጻር፣ ቀተ ስዕል ወይም ስዕል ቀት ተባለ። በ1879 ዚሱዳን ደርቡሟቜ አቃጠሉትና ሊፈርስ በቃ።
ደብሚ ፀሐይ ቍስቋም ማርያም ኹጎንደር ኹተማ በስተ ስሜን ምዕራብ ወጣ ብሎ በሚገኘው በደብሚ ፀሐይ ቁስቋም ዚተሰራ ቀተክርስቲያን ነው። ደብሚ ፀሓይ ቁስቋም በእ቎ጌ ምንትዋብ፣ ኹ1725 ዓ.ም. እስኚ በ1738ዓ.ም. ተገንብቶ ዹተጠናቀቀ ሲሆን በጊዜው 360 መስታዎቶቜ ዚነበሩት፣ በቀይና ሰማያዊ ሃር አልባሳት ያሞበሚቀ፣ እንደ ደብሚ ብርሃን ስላሎ በጥሩ ኪነት ዚተዘጋጀ፣ ኹወርቅና ኚብር ዚተሰሩ ዚቀተ ክርስቲያን ማገልገያወቜ ዚነበሩት፣ በጊዜው ዹተደነቀ ቀተ ክርስቲያን ነበር። ደብሚ ፀሐይ በተመሰሚተበት ዘመን ዚራሱ ጉልት ዹነበሹው ሲሆን ይኌውም በእብናት፣ በለሳ እና አርማጭሆ ተሰባጥሮ ይገኝ ነበርፀ ስለሆነም 260 ቀሳውስትን በስሩ ያስተዳድር ነበር፡፡ ኚህንጻ ይዘቱ አንጻር በዚሁ ዘመን በምንትዋብ ኚተገነባው ናርጋ ስላሎ ጋር ይመሳስል እንደንበር ግንዛቀ አለ።
ዚቁስቋም ግቢ ሊስት ጊዜ ጉዳት ደርሶበታል። በመጀመሪያ በ1858፣ ዓፄ ቎ዎድሮስ መቅደላ ሊያሰሩት ላሰቡት ቀተ ክርስቲያን ኚቀተክርስቲያኑ ዚተለያዩ ንዋያትን መውሰዳ቞ው ነበር። ሁለተኛው ጉዳት ዹደሹሰው በ1870ወቜ፣ ደርቡሟቜ ግቢውን በእሳት በማጋዚት ያደሚሱት ዋናው ጉዳት ነበር። በዚህ ቃጠሎ ቁስቋም ማርያም ሊፈርስ ቜሏል። ቀተክርስቲያኑ አሁን ዚያዘውን ቅርጜ ያገኘው በጣሊያኖቜ ጊዜ ሲሆን ያሁኑ መልኩ ኚድሮው እጅግ ይለያል። ዚእ቎ጌ ምንትዋብ፣ ዹልጇ ዳግማዊ እያሱ እና ልጅ ልጇ እዮዋስ አጥንቶቜ በመስታዎት ሳጥን ሆነው በዚህ ቀተክርስቲያን ይገኛሉ። ኚእሳት ዹተሹፉ ዚእ቎ጌ ምንትዋብ መገልገያዎቜ አሁን ድሚስ በቀተክርስቲያኑ ይገኛሉ።
ታሪክ ወንግሥት፡ ብርሃን፡ ሞገሳ ፣ ታሪክ፡ ዘንጉሠ፡ ነገሥት፡ አድያም፡ ሰገድ በዘመናቾው በነበሹው ፀሐፊ [[]] በግዕዝ እንደተጻፈና በኢኛትሲዮ ግዊዲ በ1895 ፣ በጣሊያን አገር እንደታተመ ኹጎን ቀርቧል። ይህ ዚንግሥት ምንትዋብና ዹልጇን ዳግማዊ ዓፄ ኢያሱን ዜና ውሎ ይተርካል። በተጚማሪ ዹዓፄ ኢያሱን ልጅ ዹዓፄ ኢዮአስን ዜና መዋዕል በተኚታዩ ገጜኊቜ አካቶ ይዟል።
ናርጋ ስላሎ ኚጣና ሐይቅ ደሎቶቜ በስፋቱ አንደኛ ኹሆነው ደቅ ደሎት ላይ በምዕራባዊ ክፍሉ ዹሚገኝ ቀ/ክርስቲያን ነው።
ቀተክርስቲያን በእ቎ጌ ምንትዋብ 1700ወቹ መጚሚሻ ላይ ዚተገነባ ሲሆን፣ እበሩ ላይ ዚሚታይቱት ስዕሎቜ ዚእ቎ጌ ምንትዋብና እንዲሁም ኢትዮጵያን በዚያው ዘመን ጎብኝቷት ዹነበሹው ዚስኮትላንድ ተጓዥ ጄምስ ብሩስ (ሃኪም ይጋቀ) ና቞ው።
እ቎ጌ ምንትዋብ በዙፋን ስሟ ብርሃን ሞገስ በ1698 ዓ.ም. ኚአባቷ ደጅአዝማቜ መንበር እና እናቷ ልዕልት እንኮይ በቋራ፣ ጎንደር ስትወለድ ዚክርስትና ስሟ ወለተ ጊዮርጊስ ነበር። እናቷ ልዕልት እንኮይ ኹዓፄ ሚናስ ዘር ዚምትወለድ እንደነበሚቜ ይጠቀሳል[1]። ምንትዋብ በ18ኛው ክፍልዘመን ኢትዮጵያ ላይ ብዙ አሻራ ትታ ዚለፈቜ ንቁ፣ ሃይለኛና ተራማጅ መሪ ነበሚቜ። ኚባሏ ዓፄ በካፋ ዘመን ጀምሮ እስኚ ልጇ ዳግማዊ ዓፄ ኢያሱ እና ልጅ ልጇ ዓፄ እዮዋስ ዘመን ድሚስ ለ40 አመታት ዚአገሪቱ እኩል መሪ ዚነበሚቜ ናት። በዚህቜ መሪ ዘመን በኢትዮጵያ ውስጥ ትልቅ ዚህንጻዎቜ ግንባታና ዚቀተክርስቲያን ድሚሰት፣ እንዲሁም ስነ ጥበብ እድገት ታይቷል። በፋሲል ግቢ ዚመጚሚሻውን ግንብ ያስገነባቜው ምንትዋብ ነበሚቜ። ኚልጆቿ ዚእድሜ አናሳነትና እራሷም በሰራቻ቞ው አንድ አንድ ስህተቶቜ ምክንያት በስልጣን በነበሚቜበት ዘመን ዹነበሹው እድገትና ሰላም እርሷ ስታልፍ አብሮ አለፏል። እንግዎህ አገሪቱ ወደ ዘመነ መሳፍንት ዚተሻገሚቜው ልክ እርሷ እንዳለፈቜ ነበር።
ዐፄ በካፋ
ኹዐፄ በካፋ ጋር ስለመገናኘቷ
ዐፄ በካፋ በህዝብ ዘንድ ክብርን ካስገኘለት ስራው አንዱ ብዙ ጊዜውን በመሰዋት፣ እራሱን ደብቆ በግዛቱ ሁሉ እዚተዘዋወሚ ስህተት ዚተሰራውን ማቃናቱ ነበር። [2] በዚህ ሁኔታ አንድ ቀን ተደብቆ ኚጣና ሃይቅ በስተ ምዕራብ ሲጓዝ ቋራ ላይ ወባ ታመመና ኚአንድ ገበሬ ቀት አሚፈ። ዚስኮትላንዱ ተጓዥ ሐኪም ይጋቀ ሲተርክ "ወጣቷ ምንትዋብ ኹመጠን በላይ ቆንጆ፣ ተግባቢና ልዝብ" [3]ዚነበሚቜ ሲሆን በካፋ ታሞ ያሚፈበት ቀት ባለቀት ልጅ ነበሚቜ[4]። ምንትዋብ ታማሚውን ንጉሥ ተንክባክባ ለጀንነት ስላበቃቜው ጳጉሜ5፣ 1716 (እ.ኀ.አ) ላይ ወደ ጎንደር ኚተማእንዳስመጣትና እንዳገባት ይዘግባል። በ1717 ዳግማዊ አጌ ኢያሱን ወለደቜ። ኹዚህ በኋላ ለ2 አመት ጎንደር ኹተማ ተቀምጣ በመካኚሉ በ1718 ወደ ወልቃይት እንድትሄድ ተደሚገ። ምንም እንኳ ኚሁለት ወር በኋላ ብትመለስም ልጇ ግን ወደ ሰሜን ሜሬ፣ ትግሬ ተልኮ በዚያ እስኚ 1730 መኖር ቀጠለ[5]።
ዚአጌ በካፋ መሞትና ዚምንትዋብ መንገሥ
አጌ በካፋ በ1722 ዓ.ም. ሲሞት ዹኹተማው ህዝብ ሞቱን ሊቀበል አልቻለም። ለዚህ ምክንያቱ ኹአሁን በፊት ንጉሱ ሳይሞት ዹሞተ በማስመሰል ህዝቡ ላይ ሜብር በመፍጠሩ ነበር። ምንትዋብም ባሏ ሲሞት ዚህዝቡን ጥርጣሬ በመጠቀም ውስጥ በማስገባትና ኚቋራ አምስት ወንድሞቿ መጥተው ዚቀተመንግስት ስልጣን እስኪጚብጡና እስኪያሚጋጉ ድሚስ ዚንጉሱን ሞት ደብቃ ቆዚቜ[6]። ኚወንድሞቿ መምጣት በኋላ እርሷና ዘመዶቿ ሆነው ዹ 7 አመት ልጇን ኢያሱን ለማንገስ ቻሉ። ኹ2 ወር በኋላ ታህሳስ 15፣ 1722 ላይ ዹልጇን ህጻን መሆን በማስታኚክ እራሷ ላይ ዘውድ በመጫን በንግሥት ሥልጣን እንደራሎነቷን አሳወጀቜ[7]። ለሚቀጥሉት 40 አመታት እርሷና ወንድሟ ወልደ ልዑል ኚንጉሥ ልጇና ልጅ ልጇ ጋር እኩል ተሰሚነት ኑሯ቞ው አገሪቱን ለማስተዳደር በቁ፡፡ አንዳንዶቜ ይህ በዝምድና ዹተተበተበ አመራርና ያስኚተለው ዹዘር ፉክክር አገሪቱን ለዘመነ መሳፍንት ያበቃ ተግባር ነበር ሲሉ ይታዘባሉ[8]።
ዚምንትዋብ አስተዳደር
ምንትዋብና ልጇ ይኚተሉት ዹነበሹው ፖሊሲ ፊት ለፊት መጋፈጥ ሳይሆን እርቅንና መስማማትን ነበር። ለዚህ ተግባር እንዲሚዳት፣ በጣም ቆንጆ ዚሚባሉ ሶስት ሎት ልጆቿን (ኚበካፋ ሞት በኋላ ካገባቜው ምልምል ኢያሱ ዚተወለዱ) በዘመኑ ኃይለኛ ለተባሉ ዚጎጥ መሪወቜ በመዳር (ወለተ እስራኀልን ለጎጃም ጩሹኛ ደጃቜ ዮሎዎቅ ወልደ ሃቢብ (1751)፣ ወይዘሮ አልጣሜን ለሰሜን ባላባት ወልደ ሃዋርያት (ዚራስ Michael Sehul ልጅ)1747 እና ወይዘሮ አስ቎ርን ለትግሬ መሪ ራስማርያም ባሪያው1761) በመዳር በግዛቷ ስላም አስፍና ነበር[9]። ንግስቲቱ በማዕኹላዊው መንግስት ሹም ሜሚት ብታደርግም ራቅ ብለው ዚሚገኙት ክፍሎቜ ግን በራሳ቞ው እንዲተዳደሩ አድርጋ ነበር። ዚኊሮሞ ቡድኖቜ ወደ ሰሜን ዚሚያሚጉትን ዘመቻ ስላቋሚጡ በደቡብ በኩል መሚጋጋት ተኚስቶ ነበር። በሌላ ጎን፣ በደቡብ ዚተወሰዱ መሬቶቜን ለማስመለስ ምንም አይነት ዘመቻ በዚህ ዘመን አልተካሄደም። ስለሆነም ኹጊዜ ወደጊዜ ራቅ ያሉ ስፍራወቜ ኢ-ጥገኝነታ቞ው እዚጎላ ሄደ። ኹነበሹው አጠቃላይ ሰላም አንጻር ልጇ እያሱ ወደ ሰሜን ዚሚያደርገው ዘመቻ ዚፖለቲካ ሳይሆን ለአደንና መሰል ክንውኖቜ ነበር[10]።
ምንትዋብና ያኚናወነቻ቞ው ስራዎቿ
በልጇና በልጅ ልጇ ዘመናት ለ40 ዓመት ስትነግስ ያኚናወና቞ቻው ስራወቜ ብዙ ነበሩ። ምንትዋብ በባህሪዋ ተራማጅና ንቁ ነበሚቜ። በቀተክርስቲያን ተነስቶ በነበሹው ዚቅባት እና ተዋህዶ ክርክር ለማስታሚቅ ያደሚገቜው ጥሚት ዚተሳካ ነበር። ስለሆነም ኹሞላ ጎደል በአስተዳደሯ ወቅት ሃይማኖታዊ ስላም ነግሶ ነበር።[11] ኚሌሎቜ መንፈሳዊ ስራዎቿ ውስጥ ብዙ አብያተ-ክርስቲያናትንና ግንቊቜን በማነጜ እንዲሁም በግሏ እዚተኚታተለቜ ድርሰቶቜን በማስደሚስ ስሟ ይጠቀሳል።
ቁስቋምን በደብሚ ፀሐይ ስለመመስሚቷ
እ቎ጌ ምንትዋብ በተለያዩ ምክንያቶቜ እራሷን ኹጎንደር ኹተማ ለማራቅ ጥሚት አድርጋለቜ። ዹዚህ ጥሚት ውጀት ኹጎንደር ኹተማ 3 ኪሎሜትር ራቅ ብሎ በሚገኘውደብሚ ፀሐይ (ቁስቋም) ያሰራቻ቞ው ህንጻወቜ ና቞ው። ዚስኮትላንድ ተጓዥጄምስ ብሩስ (ሃኪም ይጋቀ) በኒህ ህንጻወቜ አንድ ክፍል ተሰጥቶት ይኖር ነበርና ስለቁስቋም ሲጜፍ 3 ፎቅ ዹሆነ ቀተመንግስት፣ ክብ ዹሆነ ቀተክርስቲያንና ብዙ ዚተለያዩ ዚሰራተኞቜና ዘበኞቜ ቀቶቜ እንዲሁም ግብዣ ቀት በአንድ ማይል ዙርያ በታጠሚ ግቢ ይኖር እንደነበር አስፍሯል[12]። እነዚህን ቀተመንግስቶቜና ቀተክርስቲያኖቜ ኹ1723 ጀምራ በማሰራት በ1732 ነበር ያስመሚቀቻ቞ው[13]።
በግቢው ውስጥ ዹሚገኘው ቀተ ክርስቲያን፣ ደብሚ ፀሐይ ማርያም ይባላል። በጄምስ ብሩስ ግምት፣ ኢትዮጵያ ኹሚገኙ አብያተ ክርስቲያናት ሁሉ ሃብታም ዹነበሹና ብዙ ምርጥ ምስላትንና በወርቅና በብር ዚተሰሩ ዚቀተክርስቲያን መገልገያ ዕቃወቜን ዹተመላ ነበር[14]። ዚተገነባውም በአናጢዎቜመሪ በጅሮንድ ኢሳያስ እና አዛዥ ማሞ፣ አዛዥ ህርያቆሳና አዛዥ ናቡተ መሪነት ነበር። ቀተክርስቲያኑ በቀይ ሃር አሞብርቆ በዙሪያው 380 መስታውቶቜ ተተክለውት ብርቅርቅታው ጎንደር ኹተማ ድሚስ ይታይ ነበር[15]። ነገር ግን ቀተክርስቲያኑና ሌሎቜ በግቢው ዚነበሩ ህንጻወቜ በሱዳን ወራሪ መሃዲስቶቜ፣ በ1880 ተቃጠሉ። አሁን በጊቢው ዹሚገኘው ቀተክርስቲያን በዚህ ፍርስራሜ ላይ ዚተሰራ ነው።
End of preview. Expand in Data Studio
README.md exists but content is empty.
Downloads last month
90